tg-me.com/nibab_lehiwot/173
Last Update:
የእኔ ታሪክ ምዕራፍ-2)
ክፍል- 12
አሌፍ በተረጋጋ መንፈስ በቀስታ እየ ተራመደ ወደእነ ቪቪያን ቀረበ። ቪቪያን ስታየው ልቧ ክፍል አለ። ሮጣ ሔዳ ተጠምጥማበት የአባቷን ህመም አብሮ ቢያስታምማት፣ ፀጉሯን እያሻሸ አይዞሽ አባባ ደህና ይሆናሉ ቢላት በወደደች ነበር። ግን አትችልም አሌፍ ራሱ አብረን መሆን አንችልም ብሎ ግንኙነታቸውን አቋርጦታል። ስለዚህ እንደምንም ራሷን አረጋግታ ተቀመጠች። አሌፍም ቪ ምን ሆነው ነው አባባ አላት ማቲያስን ከነመፈጠሩ ረስቶ። ራሱን ስቶ ነው ብላ ዝም አለች። ስብር ባለ ፊት አይዞሽ ፈጣሪ ይጠብቀዋል ብሏት ወደ ኤልሳ ሔደ። እሷንም እንዲሁ ካፅናናት እና ከሜሮንም ጋ ትንሽ ካወሩ በኋላ ሜሮን ማቲያስን ጠርታ አስተዋወቀችው። ግን የራቢያ ልጅ እንደሆነ ለማንም አልተናገረችም።
ከ 5 ሰዓታት ጥበቃ በኋላ ሕዝቅኤል ነቃ። ቪቪያን እና ኤልሳ ለመግባት በጣም ቢፈልጉም ቀድሞ ማግኘት የፈለገው ግን አሌፍን ነበር። አሌፍ ደግሞ ወጥቶ ከሄደ ቆይቷል። ስልክም ሲደውሉ ሊያነሳ ስላልቻለ ቪቪያን እና ማቲያስን ስራ ቦታው ጋ ሔደው እንዲያመጡት ሜሮን ላከቻቸው። በጉዟቸው ላይ ስለ ቤተሰቦቻቸው በጣም ብዙ አወሩ። ቪቪያን በሜሮን ተደነቀች ። ልክ ሕዝቅኤል ለ እርሷ እየነገረ እንዳሳደጋት ሜሮንም ለማቲ እንደዛ ሙሉ ታሪኳን እየነገረች እንዳሳደገችው ተረዳች። በጣም የሚገጣጠሙ አይነት ሰወች ሆነዋል። አባዬ ግን አሌፍን ይሔንን ያክል ለምን እንደፈለገው አልገባኝም አለች ወደ ማቲያስ እየተመለከተች(በጣም ቅልል ብሏት ነው የምታወራው) አትጨነቂ ምናልባት በጣም አስፈላጊ ስለሆነባቸው ይሆናል ይልቅ እንድናገኘው ፀልይ ........
ወደ አሌፍ ቢሮ ሲገቡ ማቲያስ እንደፈራው አላገኙትም የስራ ባልደረቦቹን ሲጠይቁ ቢሮ ብዙም ሳይቆይ እንደወጣ ነገሯቸው። ቪቪያን እሱን ሳትይዝ ላትመለስ ለራሷ ቃል ገብታለች ። ና ማቲ የት እንደሚገኝ አውቃለሁ ብላው ተያይዘው ወጡ።
ሕዝቅኤል ሜሮን እና ኤልሳን በደከመ ድምፅ እያናገራቸው ነው። ኤልሲ አ...አሌፍ...ልጄ... ነው ነገሮች ከመበላሸታቸው በፊት ....እባክሽ...አስቁሚያቸው......ይላታል ድምፁ ቁርጥ...ቁርጥ እያለ ነው ከመቼውም በላይ ውስጡ ሲደክም ይሰማዋል ለሞት ዳር ዳር እያለ እንደሆነ ባይናገረውም ታውቆታል። ኤልሳ የሰማችው ነገር በጣም ቢያስደነግጣትም ለእሷ ሕዝቅኤልን ከማጣት በላይ የሚያስፈራት ነገር የለም። እንዳይሞት በጣም ፈርታለች። ዝም በል ሕዝቄ እኔ ሁሉንም ነገር አስተካክለዋለሁ.....ስታወራ ይደክምሃል....አለች እየተርበተበተች። ለእሱ ያላት ፍቅር ሁሌም ቃላት ስለሚያሳጣው ከትዕዛዟ መተላለፍ አይፈልግም ቢያንስ በዚህ ልካሳት ይላል ሁልጊዜ ዛሬም እሽ ብሏት አሌፍ እስኪመጣ ዝም አለ።...
ቪቪያን እንደገመተችው አሌፍን ብቻውን ቁጭ ብሎ ሲያስብ አገኘችው ከማቲያስ ተለይታ ወደ ፊት ተራመደች ከጀርባው እንደቆመች የሽቶዋ መዓዛ ነገረው ፊቱን ሳያዞር ቪ ይቅርታ በጣም ልብሽን እንደሰበርኩት አውቃለሁ ግን ጠልቼሽ ሳይሆን ነገሮች ከመበላሸታቸው በፊት ማስቆም ፈልጌ ነው። እናቴን አማከርኳት በጭራሽ እንደዚህ አይነት ነገር እንዳላስብ አድርጋ አሳመነችኝ። የአንቺም አባት ተመሳሳይ ነገርን ነገረሽ ያለ እነሱ ፈቃድ የተመሰረተ ህይወት ደግሞ ሊሰምር እንደማይችል ደመደምኩ። ግን አቃተኝ አባባንም ላናግራቸው እቤት መጥቼ ቀጠሮ አስይዧቸው ነበር። ለምን እንደሆነ ታውቂያለሽ ቪ አንቺን መተው እንደማልችል ልነግራቸው እና በክብር አንቺን እንዲሰጡኝ ልጠይቃቸው ነበር ......ቪቪያን ዝም ብላ እንባዋን ማፍሰስ ጀመረች።ቪ አላት ፊቱን ወደሷ አዙሮ እየተንበረከከ። ሁሉንም ነገር እንተወው ፍቅር ከ ሀይማኖት፣ ከሀገር፣ ከአለም፣ ከሁሉም ነገር ይበልጣል አንቺም በ ሀይማኖትሽ እኔም በ ሀይማኖቴ መኖር እንችላለን ዋናው መሃላችን ያለው ፍቅር ነው። ልጆችንም ቢሆን በፍላጎታቸው እንዲወስኑ እንተዋቸዋለን ። በአንቺም በ እኔም እምነት ፍቅር ከሁሉም እንደሚበልጥ የሚያስተምር አምላክ ነው ያለን። ወንድ እና ሴት ብንሆን፣ ሙስሊም እና ክርስቲያን ብንሆን፣ ፍቅር ግን ያስተሳስረናል።
ማቲ ተገርሞ ይመለከታቸዋል። ቪ የ አባትሽን ታሪክ እንዳትደግሚው እፈራለሁ አለ በውስጡ።
የቪቪያን እንባ ፈስሶ የሚያልቅ አይመስልም። ተነስ አሌፍ አባባ አንተን ብቻ ነው ማናገር የፈለገው አለች እንደ ጅረት የሚንቆረቆረውን እንባ ለማስቆም በግድ እየታገለች።
አሌፍ እንደተንበረከከ እጇን አጥብቆ ያዛት።ቪ መጀመሪያ እሽ በይኝ አብረን እንሁን እባክሽ ወደ ፍቅር አለማችን ይዤሽ ልጥፋ የራሳችንን ሕይወት ከዛሬ ጀምሮ ሀ ብለን እንደ አዲስ እንጀምር.............
ቪቪያን ደነገጠች የልብ ምቷ ፈጠነ።
ይቀጥላል........
@nibab_lehiwot
BY ሕይወትን - በገፅ
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/nibab_lehiwot/173